የአቶ ልደቱ አያሌው ሰነድ በሙሁራን ሲፈተሽ፡ ውጥንቅጥ ፖለቲካ

8 months ago
107

አቶ ልደቱ አያለው በቅርቡ ለኢትዮጵያ ችግር መፍትሄ ይሆናል ያሉትን ሃሳብ በፅሁፍ አቅርበው ሕዝብ ይወያይበት ብለዋል ይህ ሰነድ ከእዚህ ቀደም ካቀረቡት ሰነድ የተለየ ባይሆንም የሰነዱ በእዚህ ወቅት መቅረቡ እና በውስጡ የያዘው መልእክት ሲገመገም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከአማራ የህልውና ትግል ጋራ የተያያዘ ነው ለማለት የሚያስችሉ በቂ ምክንያቶች ከሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡ በአቶ ልደት አገላላፅ ፅንፈኛ ጦረኛ ብለው የሚጠሩት ፋኖ/አማራ ትግሉን አቁሞ ወደ ውይይት መደረክ መምጣት እና ላም አለኝ በሰማይ በሆነው የሽግግር መንግስት ተካፍይ እንዲሆን ይጋብዛሉ ፡፡ ሲጀመረ የሽግግር መንግስት አስተሳሳብ በአብይ ህገወጥ ነው፡፡ ያም ብቻ አይደለም ፋኖን በተለያየ መንገድ የሚደግፈውን በውጭ ነዋሪ የሆነው አማራ ፅንፈኛ ብለው በእዚህ መልኩ ይገልፁታል "ዲሞክራሲና መቻቻል በሰፈነባቸው አገራት እየኖረ ከዚያ በተፃፃሪና በአገር ቤት ከሚኖረው ሕዝብ በላይ የብሔርተኛነት፣ የፅንፈኛነት እና የጦረኛነት ፖለቲካ አራማጅና ደጋፊ መሆኑ፤" በጥቅሉ አቶ ልደቱ አያሌው ያቀረቡት ሰነድ የአማራን ትግል የማጠልሽት አላማ ብቻ ያለው ሳይሆን እየተፋፋመ የመጣውን ትግል የማኮላሽትም እና በአናቱ ውሃ የመቸለስም አላማ ያለው ነው፡፡ ለእዚህም ማሳያ የሆነው የራሳቸው ቃል ነው፡፡ የአማራ ሕዝብ ሰቆቃ እና በደል ፈጣሪ እና አራማጅ የሆነውን አብይን እና ብልፅግናን ስብስብ የመፍትሄ አካል አድርገው ማቅረባቸው ብቻ ሳይሆን ተረኛ ነኝ ያለውን አገዛዝ ተረኛ አይደለም አንድንም ብሄር አይወክለም በለዋል፡፡ ያም ሳይበቃ አማራን በጠላትነ ፈርጀውት ለ50 አመታት ሲገሉት ሲያስገድሉት ሲያፈናቅሉት ሲያሳድዱት የኖሩትን ወያኔን እና ኦነግን እንደ እራስህ አድርግህ ውደዳቸው ጣላቶችህን አይደሉም ብለው ከትበዋል፡፡ እንዲህም ይላሉ "በአሁኑ ወቅት በአራት ኪል ቤተ-መንግሥት ውስጥ የሌሉትን እና ራሳቸው የአገዛዙ የጥቃት ሰለባ የሆኑትን ህ.ወ.ሃ.ት.ን እና ኦ.ነ.ግ.ን ዘላለማዊ ጠላት አድርጏ ከመፈረጅ፣" አማራ መቆጠብ አለበት ፡፡ ይህን ሰነድ በተመለከት በረዕዮተ አማራ ተዘጋጅቶ የቀረበውን ውይይት ዕውነት ሚዲያ ወደ እናተ ይዞ ቀርቧል ፡ አዳምጡት ፡ ተነጋገሩት ፡ ጠይቁ ፡፡ ዕውነት ሚዲያ ፡

Loading comments...