አሰብ እና አማራ ፡ የአሜሪካ የወያኔ እና የአብይ ቁማር ሲጋለጥ ፡ በዶር ደብሩ ነጋሽ

1 year ago
137

አሰብ በአጠቃላይ የአሁኗ ኤርትራ የጥንቷ ባሕረ ነጋሽ በሁሉም መስክ የኢትዮጵያ አካላ ነች፡ ሕዝቦቿም ከሌላ ምድር የመጡ ሳይሆን የቤጌምድር፤ የወሎ፡ የጎጃም እና የአፋር ሕዝቦች ናቸው፡፡ ነገር ግን በአካባቢው ለዘመናት በተካሂደው ጦርነት ዛሬ ኤርትራ ሉአላዊ አገር እንድትሆን አድርጓታል ፡፡ ይህ ክስተት የኤርትራ እና የኢትዮጵያን ፍላጎት ሳይሆን ዘመናት ያስቆጠረው ጦረነት የወለደው ክስተት ነው፡፡ ኤርትራዊያ ለእናት አገራቸው ብዙ ደም ከፍለዋል በተጨማሪም ኤርትራ ከእናት አገሯ እንድትቀላቀል ኤርትራዊያን ብዙ ደም ገብራዋል፡፡ ነገር ግን ልእለ ኃያላን አገራት በተለይ አሜሪካ አካባቢውን ለመቆጣጠር ባላት ፍላጎት ከጅምሩ ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንድትኘጠል ይህ ነው የማይባል ወታደራዊ ስራ ሰርተዋል፡፡ ከዚህም አንዲ የወያኔን የማስገንጠል አጀንዳ መደግፍ ነው ፡፡

ዛሬ ከቀዝቃዛው የአለም ጦርነት በኋላ በተከተሰው ጂኦፖለቲክስ አሰላለፍ የተደናገጠችው አሜሪካ የቀይ ባሕርን ከሶቬት እና ከቻይና ተፅእኖ ለማላቀቅ አብይን እና ወያኔ እንደ መሳሪያ በመጠቀም በኤርትራ ላይ ጦርነት በማወጅ እና ኢሳያሳን በማሶገድ ቀይ ባሕርን ለመቆጣጠር ሴራ በማሴር ላይ ናቸው ፡፡ አብይም ሆነ ወያኔ ድብቅ አጀዳቸውን ለማስፈፀም ይህን የአሜሪካ እቅድ ተቀብለው በተግባር ለማዋል የጦርነት አታሞ የየጎሰሙ ይገኛሉ፡፡

ዛሬ አማራው እና መላው ኢትዮጵያ ከወያኔ ፡ ከአብይ እና ከአሜሪካ በላይ የካፋ ጠላት የለውም ፡፡ አብይ ( ኦሮሙማ) የተሰጠውን ስልጣን በመጠቀም አማራን ለማጥፋት ብሎም ለማዳከም የማይቆፍረው ጉድዷድ የለም ፡ ወያኔ የሰላሳ አመቱ ግፍ እና በደል አልበቃ ብሏት ካንዴም ሶስቴ በአማራው ላይ ታሪክ ይቅር የማይለው አውዳሚ ጦርነት አድርጋለች ፡ አሜሪካም የአማራ ሞት ሞት ሳይመስላት አብይ እና ወያኔን በሞራል በገንዘብ በመደገፍ ላይ ትገኛለች፡፡

ዛሬ ደግሞ አማራን ጨምሮ በኢሳያስን ላይ አሰብን ሰበብ አደርገው ጦርነት ክፈቱ እያሉ ነው ፡፡ ይህ ሴራ የአማራን ሕዝብ ሆነ መላው የኢትዮጵያን ሕዝብ በማናቸውም መንግድ የማይጠቅም እና ዳግማዊ ዩክሬን በምስራቅ አፍሪካ የመክፈት ጉዳይ ነው፡፡ ይህ በተመለከተ ዶር ደብሩ ነጋሽ ከዕውነት ሚዲያ ጋር ቆይታ አድርጓል ተከታተሉት ፡፡
ተጨማሪ ንባብ፡ https://www.theepochtimes.com/has-the-west-already-lost-control-of-its-most-vital-sea-route_5359718.html

Loading comments...